Posts

Showing posts from August, 2019

ትንሣኤ ክርስቶስ በሊቃውንት አንደበት – ካለፈው የቀጠለ

Image
“ሕማምን፣ ሞትን ገንዘብ አደረገ፤ በሥጋው የሞተው ሞትም የእኛን ባሕርይ በመዋሐዱ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ተዋሕዶውን አስረዳ፤ ሞት ሰው የመኾን ሥራ ነውና፡፡ ከሙታን ተለይቶ መነሣትም አምላክ የመኾን ሥራ ነውና፤ እነዚህ ሁለት ሥራዎችን /ሞትንና ትንሣኤን/ እናውቃለን፤”  (ቅዱስ ቄርሎስ፣ ሃይ. አበ. ፸፪፥፴፭)፡፡ “በሥጋ ሞተ እንዳልን ዳግመኛ በሥጋ ተነሣ እንላለን፤ ስለ ትንሣኤም የእርሱ ገንዘብ እንደ ኾነ፤ ሙስና መቃብርም እንዳላገኘው ይነገራል፡፡ ይህ ለመለኮት አይነገርም፤ የተነሣው ሥጋው ነው እንጂ፤”  (ዝኒ ከማሁ ፸፱፥፱)፡፡ “የሞትን ሥልጣን አጠፋ፤ ዲያብሎስንና ኃይሉን (ኃጢአትን) ሻረ፡፡ የብረት መዝጊያዎችን ሰበረ (ፍዳ መርገምን አጠፋ)፡፡ ሲኦልን በዘበዘ፡፡ የጣዖት ቤቶችን አፈረሰ፡፡ የምሕረትን በር ከፈተ፤ ይህችውም በደሙ የከበረች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ለዂሉ የዘለዓለም ሕይወት መገኛ የሚኾን ልጅነት የተገኘበት ሥጋውን ደሙን ሰጠን፤”  (ቅዱስ ቴዎዶስዮስ፣ ሃይ. አበ. ፹፫፥፮)፡፡ “ለእኛስ እግዚአብሔር ቃል በባሕርየ መለኮቱ እንደ ታመመ፤ እንደ ሞተ፤ እንደ ተቀበረ ልንናገር አይገባንም፡፡ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ ሞት የሌለበት እንደ ኾነ፤ መድኀኒታችን በሚኾን በሞቱና በሦስተኛው ቀንም በመነሣቱ ትንሣኤን እንደ ሰጠን እናምናለን፡፡ የሞተ እርሱ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና፡፡ ዂሉን የሚችል እርሱ ካልተነሣ፣ የችሎታ ዂሉ ባለቤት እርሱ የሌለ ከኾነ፣ እንኪያስ ትንሣኤም ሐሰት ነዋ! ት ንሣኤም ሐሰት ከኾነ ሃይማኖታችን ከንቱ ነው፡፡ እንኪያስ አይሁድንም እንመስላቸዋለን፡፡ ሰው እንደ መኾኑ በሥጋ ባይሞትስ በሞት ላይ ሥልጣን ያለው አምላክ እንደ መኾኑ ሞትን ባላጠፋ ነበር፡፡ የአዳም የዕዳ ደብዳቤም ከእግዚአብሔርና ከ...

ትንሣኤ ክርስቶስ በሊቃውንት አንደበት – የመጀመሪያ ክፍል

Image
በየጊዜያቱና በየዘመናቱ የተነሡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ከዚህ ቀጥሎ የተገለጠውን ትምህርትና ምስክርነት ሰጥተዋል፤ “ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ሲኦልን ረግጦ፣ በሞቱ ሞትን አጠፋው፤ በሦስተኛው ቀንም ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ‹አባት ሆይ አመሰግንሃለሁ፥› ብሎ ሥግው ቃል አመሰገነ፤”  (እልመስጦአግያ ዘሐዋርያት ፭፥፩)፡፡ “እንደ ሞተ እንዲሁ ተነሣ፤ ሙታንንም አስነሣ፡፡ እንደ ተነሣም እንዲሁ ሕያው ነው፤ አዳኝ ነው፡፡ በዚህ ዓለም እንደ ዘበቱበት፣ እንደ ሰደቡት እንዲሁ በሰማይ ያሉ ዂሉ ያከብሩታል፤ ያመሰግኑታል፡፡ ለሥጋ በሚስማማ ሕማም ተሰቀለ፤ በእግዚአብሔርነቱ ኃይል ተነሣ፡፡ ይኸውም መለኮቱ ነው፡፡ ወደ ሲኦል ወርዶ ነፍሳትን ማረከ፤”  (ቅዱስ ሄሬኔዎስ፣ ሃይ. አበ. ፯፥፳፰-፴፩)፡፡ “እንዲህ ሰው ኾኖም ሰውን ፈጽሞ ያድን ዘንድ ታመመ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፡፡ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤”  (ዘሠለስቱ ምዕት ፲፱፥፳፬)፡፡ “ሞትን ያጠፋው፤ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ የሞት ሥልጣን የነበረው ዲያብሎስን የሻረው እርሱ ነው፡፡ ሰው የኾነ፤ በሰው ባሕርይ የተገለጠ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሔር ያደረበት ዕሩቅ ብእሲ አይደለም፡፡ ሰው የኾነ አምላክ ነው እንጂ፡፡ ፈጽሞ ለዘለዓለሙ በእውነት ምስጋና ይገባዋል፤”  (ቅዱስ አትናቴዎስ፣ ሃይ. አበ. ፳፭፥፵)፡፡ “ሥጋው በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሣ፤ ነፍሱም በሲኦል ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን ፈታች፡፡ በዚያም ሰዓት የጌታችን ሥጋው በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ መቃብራት ተከፈቱ፤ ገሃነምን የሚጠብቁ አጋንንትም ባዩት ጊዜ ሸሹ፡፡ የመዳብ ደጆች ተሰበሩ (ሊቃነ አጋንንት፣ ሠራዊተ አጋንንት ድል ተነሡ)፡፡ የብረት ቍልፎቿም ተቀጠቀጡ (ፍዳ መርገም ጠፋ)፡...

ዕርገተ ሥጋ፤ ርደተ ቃል

Image
ዲያቆን ዮሴፍ በቀለ የቃልን ከልዕልና ወደ ትሕትና መምጣት፤ የሥጋን ከትሕትና ወደ ልዕልና መውጣት ስናስብ እጅግ ያስደንቀናል! የመጀመሪያው የሰው ልጆች አባት ከክብር ወደ ሓሳር መምጣት ፍጥረትን ሁሉ ያስገረመ ጉዳይ ነበር፤ የሁለተኛው አባታችን ከልዕልና ወደ ትሕትና መምጣት ዳግም አስገረመን፤ ሁለቱም ይሆናሉ ብለን ያልጠበቅናቸው ክሥተቶች ናቸውና። የእግዚአብሔርን ፍቅር እስኪ ተመልከቱት! አዳምን በልጅነት አከበረው፤ ይህ የመጀመሪያው የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት ነው፤ ሙት የነበረውን ባሕረ የሰብእ ምድራዊት ሕይወቱን በሰማያዊ የልዕልና ሕይወት ለወጠለት። ይህንንም ሲያደርግ የበለጠ ተስፋ በማድረግ ነው እንጅ እንዲያው ያለ ምክንያት አልነበረም፤ ወይሁቦ እግዚአብሔር አምላክ መንበረ ዳዊት አቡሁ ወይነግሥ ለቤተ ያዕቆብ ለዓለም፤ እግዚአብሔር አምላክም የዳዊትን የአባቱን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ለዘለዓለም ይነግሣል››፡፡ ይህ የመጨረሻውን የተስፋ ምሥጢር የያዘ ቃል ነው፤(መጨረሻነቱ ለሕገ ተሰብኦ ነው እንጅ ለዘለዓለሙ እንዳልሆነ ግልጽ ነው)። ከመሬት ዐፈር ያበጀው ምድራዊ ፍጡር አዳም፤ በተረገመባት ዕለት ‹‹ኦ! አዳም መሬት አንተ ወትገብእ ውስተ መሬት፤ አዳም ሆይ! አንተ መሬት ነህ ወደ መሬትነትህ ትመለሳለህ ›› ብሎ ነገረው፡፡ በዚህም የሥጋውን ፈቃድ ትቶ በነፍሱ ፈቃድ ይኖር ነበር፤ ይህ ለነፍሱ የተሰጠው ቃል ኪዳን ነው፤ ሥጋ የራሷን ፈቃድ ትታ በነፍስ ፈቃድ ትሄዳለች፤ ነፍስ ደግሞ ያላትን ሰማያዊ ጸጋዋን ከሥጋዋ አዋሕዳ ትኖራለች። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወደዚህ ዓለም መጥቶ የጠፋውን የሰው ልጅ ክብር መለሰ፤ ሳይገባቸው የነገሡትንም ቀጣቸው፤ያለ አግባብ የተዋረዱትን ከፍ ከፍ ሊያደርጋቸውም ፍጹም ሰው ሆኗል። ከተ...